ወደ ዋና ይዘት ዘለው ይሂዱ


ከጥቁር ሰማይ ስር

በእንዳለጌታ ከበደ




ጥዋት ጥዋት፣ ወደ ቢሮ ለመሄድ - መታጠፊያው ጋ ሲደርስ - እተለመደ ቦታዋ ቁጭ ብላ የሚያጉተመትም በሚመስል ድምጿ ያለማቋረጥ ስታወራ ይሰማታል፡፡ የአራት ልጆች እናት የሆነችዋን የኔ ቢጤ፡፡
የእናታቸውን ያህል ባይሆንም ጎስቁለዋል፡፡ እንደ ምጣድ ማሰሻ የቀድሞ ከለሩ ያልታወቀ ከነቴራ ለብሰዋል - ከወገባቸው በላይ፡፡ ከመሃከላቸው አንዳቸውም ቃጭል አንጠልጥለው አልተወለዱም፡፡
. . . በማያውቀው ቋንቋ ታወራቸዋለች፡፡
ልጆቿ አይመልሱላትም፡፡ እርስ በርሳቸው ሲጨዋወቱ በአዲስ አበባ አማርኛ ነው የሚግባቡት፡፡
እንዲህ በከንቱ ጉንጭዋን የምታለፋው በውስጡ ያደረውን ጩዋሂ መንፈስ ላለማዳመጥ ይሆን? ብሎ ያስባል
ጤንነቷን የማይጠራጠር የለም፡፡ አንዳንዶች ፥ ስለ ልጆቿ የወደፊት ዕጣ ፈንታ ማሰላሰል ስታበዛ ይሆን ያተሳሰብ ማዛንዋ የተዛባው? ይላሉ፡፡
ሁልጊዜ ያልተለመደ ነገር ስታደርግ ያጋጥመዋል፡፡ እጇ ላይ የተገኘን ማንኛውም ነገር ለአራት አካፋፍላ ለልጆች ታድላቸዋለች፡፡ ለራሷ የምታደርገው አይኖራትም፡፡ ከሲታ ናት ደግሞ፤ ያለ እህል ውሃ ለመኖር ሙከራ የጀመረች እስኪመስል ድረስ፡፡
ሳንቲም ተወርውሮ እግሯ ስር ያረፈ እንደሆነ ቅጭልጭልታውን ሰምታ እንኳን ቀና አትልም፡፡ ማንንም አይታይም - አገጯን ጉልበቷ ስር ደብቃ ነው፤ ቀኑን ውላ የምታመሸው፤ የምታነጋውም! መንገድ ዳር፡፡
እሷ ካለችበት ፈንጠር ብሎ - አንድ ክፉ የማይመስል - ዘባተሎ ለባሽ ጎልማሳ - በጠባቂነት መንፈስ ዓይኑን ያንከራትትባቸዋል፡፡ በየመንገዱ የሰበሰባቸው ቁርጥራጭ ሲጋራዎች ከኪሱ እያወጣ ያጨሳል፡፡
የልጆቿ አባት ይሆን? . . . ወይስ ወደ ጎዳና ከወጣች በኋላ የተወዳጃት ጊዜያዊ ባል?! . . . ወይስ ከክፉ ሊታደጋት ተከትሏት የመጣ . . . ? ወይስ ለነፍሱ ያደረና እነዚህን ሕጻናት ታድጎ በቅዱሳን መዝገብ ስሙን ለማስጻፍ የሚተጋ ይሆን?
ከሁላቸውም የምታንሰዋ ሕጻን ዕለተሞቷ የተቃረበ ገመምተኛ ነው የምትመስል፡፡ ሁለት ዓመት ይሆናታል፡፡ የምትተልቀዋ ስድስት እንቁጣጣሾች አክብራለች፡፡ ከእናቷ ጎን ፈቀቅ ሳትል ወጭ ወራጁን ታጤናለች፡፡ ከአጠገቧ አንድ ሰው ያለፈ እንደሆነ ‘ጋሽዬ ለዳቦ?’ ብላ ተለሳልሳ ትለምናለች፡፡
የተሰጣትን አጠራቅማ ሃምሳ ሳንቲም ሲሞላ ዳቦ ለመግዛት ሩጫዋን ታቀጥነዋለች፡፡ ታናናሾቿም ከተደበቀችበት ክንፍ አፈትልካ እንደምትወጣ ጫጩት ከእናታቸው ጉያ ሾልከው ይከተሉዋታል፡፡
የገዛችውን ዳቦ እናቷ እጅ ላይ ታኖረዋለች፡፡ እናት ዳቦውን ለአራት ታካፍለዋለች፡፡ ለራሷ የምታስቀረው የላትም፡፡
ልጆቿም እንድትበላላቸው አያባብሏትም፡፡
አንዳንዴ፣ ስለ እናታቸው ምን ያስቡ ይሆን? ብሎ ያስባል፡፡ ሳይሳለማቸውና ድምጹን ሳያስደምጣቸው ማደር አይሆንለትም፣ አንጀቱ እየተንሰፈሰፈ በደስታ ይጨብጣቸዋል፡፡ እጁን ለመንካት ይሩዋሩዋጣሉ - እየተጩወጩዋሁ፡፡
እናትየው ይህን ሁሉ አታይም፡፡ ቀና ብሎ የው ዓይን ማየት የሚሆንላት አይመስልም፡፡ ብታያቸው ለመደሰቷ ምክንያት መሆን ቢችል ደስ ይለዋል፡፡
ፊገግታ ፊቷ ላይ ሲጫወት ምን እንደሚመስል ማየት ያልፈለገበት ጊዜ ይኖር ይሆን?
ማታ፡፡
ሳንቲም ፍለጋ ኪሶቹን ደባበሰ፡፡ ድፍን አምስት ብር ተገኝታለች፡፡ ዙሪያውን ቃኘ፡፡ ያልተዘጉ ሱቆች አይታዩም፡፡ የት ይዘርዝረው?
ለአራት ተዘጋጅታ የነበረች ብር ናት፡፡ ምሳ ሳይበላ ነው የዋለው፡፡ ሳይበላ ስለዋለ ነው መሰል ከተራራ ላይ እየተንከባለለ እንደሚወርድ በርሜል ሆዱ ሲያጉረመርም ይሰማዋል፡፡ ብሩን የት ይዘርዝረው?
የተቻኮሉ መገደኞች በጥርጣሬ እያስተዋሉት ይተላለፋሉ፡፡ ግን ማንንም ‘ዝርዝር ከያዛችሁ ተቸገሩልኝ’ ብሎ መጠየቅን አልፈለገም፡፡
“ምሳና እራት ሳልበላ ብቀር ምን ይጎድልብኛል?” ብሎ ሆዱን ሲደልል ቆየና አምስት ብሩን አወጣ፡፡ አወጣና ሌላ ጊዜ እንደሚያደርገው አጠገባቸው ጣል አድርጎ ‘ደህና እደሩ’ ማለቱን ብቻ አልፈለገውም፡፡
አምስት ብሩን በእናትየው መዳፍ ላይ አኖረው፡፡
ፈገግታ አላሳየችውም፡፡
አላየችውምም፡፡ ድምጿም አልተደመጠ፡፡
ትልቋ ልጅ ብቻ ናት - በእጃቸው ትልቅ ነገር እንደገባ የገባት፡፡ እንደመፈንደቅም እንደመደንገጥም ብላ የተኙትን ቀሰቀሰቻቸው፡፡ ለማንቃት አልተቸገረችም፡፡ ጠባቂያቸውን ግን ተወችው፡፡ ስጋውን ለእንቅልፍ አሳልፎ ሰጥቷል፡፡
አቀማመጣቸውን ልብ ብሎ ላየ እናትየው እንስራ ትመስላለች፡፡ ሕጻናቶቿ ደግሞ እንስራው ተንሸራትቶ እንዳይሰበር ደግፈው የያዙት ጠጠሮች! . . .
እናትየው እጇ ላይ የገባውን አምስት ብር ለሁለት ከፈለችው፡፡ የከፈለቻቸውን የብር ክፍልፋዮች በሚያስገርም ፍጥነት እንደገና ቀዳደደቻቸው፡፡ ሁለት ሶስት ባልሞላ ደቂቃ ውስጥ ለልጆቿ አከፋፈለቻቸው፡፡
ትልቅዬዋ ለምቦጭዋን ጥላ በእጇ የነበረውን ሳንቲም እናቷ እናት ላይ በተነችው፡፡ “ብዙ ዳቦ የሚገዛ፣ ሁልጊዜ እንዳይርበን የሚያደርግ፣ ብር ነው ኮ እንደዚያ የማይጠቅም ያደረግሽው!” አለቻት ሳግ እየናነቃት፡፡
እናት የተባለችው ያልገባት ይመስል ልጇ ላይ አተኮረችባት፡፡ መፅዋቹም ትርጉሙን ባልተረዳችው አተያይ ሲያያት አገኘችው፡፡
እንደተያዩ ቆዩ፡፡ ትናንሽ ዓይኖቹ እንባን ያዘንቡ ጀመር፡፡ እንባው እየንሸራተተ - በጠይም ፊቱ ላይ መስመር እያበጀ - ወደ አፉ ደረሰ፡፡
ይሄ ሲሆን አምስት ብሩን የሸረካከተችው እናት ልብ ብላ አየችው፡፡
መፅዋቹ መንቀሳቀስ ጀመረ፡፡
የሚንቀሳቀስ ጥላ መስሎ በዝግታ እየተጓዘ ወደ ጨለማው ሆድ ውስጥ ገባ፡፡
ቅርፁ እስኪርት ድረስ በዓይኗ ሸኘችው፡፡
ከዚያስ በኋላ . . .
ሌቱን በሙሉ - በታላቅ ምሬት - ባለተለመደ አጩዋጩዋህ ስትንሰቀሰቅ አደረች፡፡ አምስት ብሩን

ያለ አገልግሎት
ስላስቀረችው ሊሆን ይችላል፡፡ ያቺ ብር ርሃቧን ልታስወግድበት ትችል እንደነበር ተገንዝባ ይሆናል፡፡ ወይም የዚያን መፅዋች እንባ ስታይ አንድ ነገር እንዲታወሳት ምክንያት ሆኖ ይሆናል፡፡
ለምን እንዲህ እንዳደረገች
የጠየቃት አልነበረም
ጥዋት ጥዋት፣ ወደ ቢሮ ለመሄድ - መታጠፊያው ጋ ሲደርስ - እተለመደ ቦታዋ ቁጭ ብላ የሚያጉተመትም በሚመስል ድምጿ ያለማቋረጥ ስታወራ ይሰማታል፡፡ የአራት ልጆች እናት የሆነችዋን የኔ ቢጤ፡፡
የእናታቸውን ያህል ባይሆንም ጎስቁለዋል፡፡ እንደ ምጣድ ማሰሻ የቀድሞ ከለሩ ያልታወቀ ከነቴራ ለብሰዋል - ከወገባቸው በላይ፡፡ ከመሃከላቸው አንዳቸውም ቃጭል አንጠልጥለው አልተወለዱም፡፡
. . . በማያውቀው ቋንቋ ታወራቸዋለች፡፡
ልጆቿ አይመልሱላትም፡፡ እርስ በርሳቸው ሲጨዋወቱ በአዲስ አበባ አማርኛ ነው የሚግባቡት፡፡
እንዲህ በከንቱ ጉንጭዋን የምታለፋው በውስጡ ያደረውን ጩዋሂ መንፈስ ላለማዳመጥ ይሆን? ብሎ ያስባል
ጤንነቷን የማይጠራጠር የለም፡፡ አንዳንዶች ፥ ስለ ልጆቿ የወደፊት ዕጣ ፈንታ ማሰላሰል ስታበዛ ይሆን ያተሳሰብ ማዛንዋ የተዛባው? ይላሉ፡፡
ሁልጊዜ ያልተለመደ ነገር ስታደርግ ያጋጥመዋል፡፡ እጇ ላይ የተገኘን ማንኛውም ነገር ለአራት አካፋፍላ ለልጆች ታድላቸዋለች፡፡ ለራሷ የምታደርገው አይኖራትም፡፡ ከሲታ ናት ደግሞ፤ ያለ እህል ውሃ ለመኖር ሙከራ የጀመረች እስኪመስል ድረስ፡፡
ሳንቲም ተወርውሮ እግሯ ስር ያረፈ እንደሆነ ቅጭልጭልታውን ሰምታ እንኳን ቀና አትልም፡፡ ማንንም አይታይም - አገጯን ጉልበቷ ስር ደብቃ ነው፤ ቀኑን ውላ የምታመሸው፤ የምታነጋውም! መንገድ ዳር፡፡
እሷ ካለችበት ፈንጠር ብሎ - አንድ ክፉ የማይመስል - ዘባተሎ ለባሽ ጎልማሳ - በጠባቂነት መንፈስ ዓይኑን ያንከራትትባቸዋል፡፡ በየመንገዱ የሰበሰባቸው ቁርጥራጭ ሲጋራዎች ከኪሱ እያወጣ ያጨሳል፡፡
የልጆቿ አባት ይሆን? . . . ወይስ ወደ ጎዳና ከወጣች በኋላ የተወዳጃት ጊዜያዊ ባል?! . . . ወይስ ከክፉ ሊታደጋት ተከትሏት የመጣ . . . ? ወይስ ለነፍሱ ያደረና እነዚህን ሕጻናት ታድጎ በቅዱሳን መዝገብ ስሙን ለማስጻፍ የሚተጋ ይሆን?
ከሁላቸውም የምታንሰዋ ሕጻን ዕለተሞቷ የተቃረበ ገመምተኛ ነው የምትመስል፡፡ ሁለት ዓመት ይሆናታል፡፡ የምትተልቀዋ ስድስት እንቁጣጣሾች አክብራለች፡፡ ከእናቷ ጎን ፈቀቅ ሳትል ወጭ ወራጁን ታጤናለች፡፡ ከአጠገቧ አንድ ሰው ያለፈ እንደሆነ ‘ጋሽዬ ለዳቦ?’ ብላ ተለሳልሳ ትለምናለች፡፡
የተሰጣትን አጠራቅማ ሃምሳ ሳንቲም ሲሞላ ዳቦ ለመግዛት ሩጫዋን ታቀጥነዋለች፡፡ ታናናሾቿም ከተደበቀችበት ክንፍ አፈትልካ እንደምትወጣ ጫጩት ከእናታቸው ጉያ ሾልከው ይከተሉዋታል፡፡
የገዛችውን ዳቦ እናቷ እጅ ላይ ታኖረዋለች፡፡ እናት ዳቦውን ለአራት ታካፍለዋለች፡፡ ለራሷ የምታስቀረው የላትም፡፡
ልጆቿም እንድትበላላቸው አያባብሏትም፡፡
አንዳንዴ፣ ስለ እናታቸው ምን ያስቡ ይሆን? ብሎ ያስባል፡፡ ሳይሳለማቸውና ድምጹን ሳያስደምጣቸው ማደር አይሆንለትም፣ አንጀቱ እየተንሰፈሰፈ በደስታ ይጨብጣቸዋል፡፡ እጁን ለመንካት ይሩዋሩዋጣሉ - እየተጩወጩዋሁ፡፡
እናትየው ይህን ሁሉ አታይም፡፡ ቀና ብሎ የው ዓይን ማየት የሚሆንላት አይመስልም፡፡ ብታያቸው ለመደሰቷ ምክንያት መሆን ቢችል ደስ ይለዋል፡፡
ፊገግታ ፊቷ ላይ ሲጫወት ምን እንደሚመስል ማየት ያልፈለገበት ጊዜ ይኖር ይሆን?
ማታ፡፡
ሳንቲም ፍለጋ ኪሶቹን ደባበሰ፡፡ ድፍን አምስት ብር ተገኝታለች፡፡ ዙሪያውን ቃኘ፡፡ ያልተዘጉ ሱቆች አይታዩም፡፡ የት ይዘርዝረው?
ለአራት ተዘጋጅታ የነበረች ብር ናት፡፡ ምሳ ሳይበላ ነው የዋለው፡፡ ሳይበላ ስለዋለ ነው መሰል ከተራራ ላይ እየተንከባለለ እንደሚወርድ በርሜል ሆዱ ሲያጉረመርም ይሰማዋል፡፡ ብሩን የት ይዘርዝረው?
የተቻኮሉ መገደኞች በጥርጣሬ እያስተዋሉት ይተላለፋሉ፡፡ ግን ማንንም ‘ዝርዝር ከያዛችሁ ተቸገሩልኝ’ ብሎ መጠየቅን አልፈለገም፡፡
“ምሳና እራት ሳልበላ ብቀር ምን ይጎድልብኛል?” ብሎ ሆዱን ሲደልል ቆየና አምስት ብሩን አወጣ፡፡ አወጣና ሌላ ጊዜ እንደሚያደርገው አጠገባቸው ጣል አድርጎ ‘ደህና እደሩ’ ማለቱን ብቻ አልፈለገውም፡፡
አምስት ብሩን በእናትየው መዳፍ ላይ አኖረው፡፡
ፈገግታ አላሳየችውም፡፡
አላየችውምም፡፡ ድምጿም አልተደመጠ፡፡
ትልቋ ልጅ ብቻ ናት - በእጃቸው ትልቅ ነገር እንደገባ የገባት፡፡ እንደመፈንደቅም እንደመደንገጥም ብላ የተኙትን ቀሰቀሰቻቸው፡፡ ለማንቃት አልተቸገረችም፡፡ ጠባቂያቸውን ግን ተወችው፡፡ ስጋውን ለእንቅልፍ አሳልፎ ሰጥቷል፡፡
አቀማመጣቸውን ልብ ብሎ ላየ እናትየው እንስራ ትመስላለች፡፡ ሕጻናቶቿ ደግሞ እንስራው ተንሸራትቶ እንዳይሰበር ደግፈው የያዙት ጠጠሮች! . . .
እናትየው እጇ ላይ የገባውን አምስት ብር ለሁለት ከፈለችው፡፡ የከፈለቻቸውን የብር ክፍልፋዮች በሚያስገርም ፍጥነት እንደገና ቀዳደደቻቸው፡፡ ሁለት ሶስት ባልሞላ ደቂቃ ውስጥ ለልጆቿ አከፋፈለቻቸው፡፡
ትልቅዬዋ ለምቦጭዋን ጥላ በእጇ የነበረውን ሳንቲም እናቷ እናት ላይ በተነችው፡፡ “ብዙ ዳቦ የሚገዛ፣ ሁልጊዜ እንዳይርበን የሚያደርግ፣ ብር ነው ኮ እንደዚያ የማይጠቅም ያደረግሽው!” አለቻት ሳግ እየናነቃት፡፡
እናት የተባለችው ያልገባት ይመስል ልጇ ላይ አተኮረችባት፡፡ መፅዋቹም ትርጉሙን ባልተረዳችው አተያይ ሲያያት አገኘችው፡፡
እንደተያዩ ቆዩ፡፡ ትናንሽ ዓይኖቹ እንባን ያዘንቡ ጀመር፡፡ እንባው እየንሸራተተ - በጠይም ፊቱ ላይ መስመር እያበጀ - ወደ አፉ ደረሰ፡፡
ይሄ ሲሆን አምስት ብሩን የሸረካከተችው እናት ልብ ብላ አየችው፡፡
መፅዋቹ መንቀሳቀስ ጀመረ፡፡
የሚንቀሳቀስ ጥላ መስሎ በዝግታ እየተጓዘ ወደ ጨለማው ሆድ ውስጥ ገባ፡፡
ቅርፁ እስኪርት ድረስ በዓይኗ ሸኘችው፡፡
ከዚያስ በኋላ . . .
ሌቱን በሙሉ - በታላቅ ምሬት - ባለተለመደ አጩዋጩዋህ ስትንሰቀሰቅ አደረች፡፡ አምስት ብሩን

ያለ አገልግሎት
ስላስቀረችው ሊሆን ይችላል፡፡ ያቺ ብር ርሃቧን ልታስወግድበት ትችል እንደነበር ተገንዝባ ይሆናል፡፡ ወይም የዚያን መፅዋች እንባ ስታይ አንድ ነገር እንዲታወሳት ምክንያት ሆኖ ይሆናል፡፡
ለምን እንዲህ እንዳደረገች
የጠየቃት አልነበረም

አስተያየቶች

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

ያማል! ገጣሚ ሰለሞን ሳህለ

እንደነገርኩሽ… የሚወዱትን ሰው - ቀጥሮ እንደመጠበቅ፣ የነፍሰ ጡርን ሞት - አይቶ እንደመሳቀቅ፣ ባልታሰበ ናዳ - ተመትቶ እንደመድቀቅ፣ ከተስፋ ጉልላት - ተገፍቶ እንደመውደቅ፣ ታምር በበዛባት - በዚህች ቧልተኛ ዓለም፣ ከዚህ የበለጠ - ምንም ህመም የለም፡፡ አውቶብሱ ያማል፣ ሚኒባሱ ያማል፣ ላዳ ታክሲው ያማል፣ የማይጎል የሰው ጎርፍ ደራሽ ማዕበሉ፣ የእንባ ቅጥልጥሉ፣ ምን ብዬ ልንገርሽ - ያማል ይሄ ሁሉ፡፡ እና እንደነገርኩሽ… የሚወዱትን ሰው ቀጥረው ካረፈደ፣ የሚያፈቅሩትን ሰው ቀጥረው ካረፈደ፣ ነገር ተበላሸ - ህመም ተወለደ፡፡ ጨጓራ በገነ፣ እሳት በእንፋሎት መልክ በእህታ ተነነ፡፡ የሚሆነው ሳይሆን የማይሆነው ሆነ፡፡ ሁሉም ተቀይሮ ተተካ በሲቃ፣ ምን ብዬ ልንገርሽ ይህም ያማል በቃ፡፡ ወጪ ተራማጁ፣ አስመሳይ ሰጋጁ፣ ፀሐዩ ዝናቡ፣ የለምን ምክንያት የለምን ሰበቡ፣ ተቆራጭ አበባ ሊቆረጥ ማበቡ፣ ውል የለሽ ደመና ተራራ መክበቡ፣ እልፍ አዕላፍ ኮከብ ጨረቃን ማጀቡ፣ ደግሞ ለእሷ ግጥም እናቷን ጨረቃ፣ ምን ብዬ ልንገርሽ ይህም ያማል በቃ፡፡ እና እንደነገርኩሽ… ጉንጭ የማትሞላ ኬክ 10 ብር የሸጠ፣ የካፌ አሳላፊ ወደ እኔ አፈጠጠ፡፡ ዘይት የነካውን መንታ እጁን አጣምሮ፣ ምን ልታዘዝ ይላል ቁልቁል አቀርቅሮ፡፡ ምን ልታዘዝ ይላል… እንዴት ቅጥሉ ሰው ቅጥሉን ሰው ያዛል፣ ማኪያቶ ልዘዝ…? ካፑቺኖ ልዘዝ…? ጥቁ ቡና ልዘዝ…? ለምን ሰው አላዝም… መታዘዝ መናዘዝ ርግማን የሆነው፣ ካፌውን ሲያሳልፍ፣ ራሱ ግን የሚያልፍ፡፡ ቁልቁል አቀርቅሮ፣ ሞቱን ባንገት ቀብሮ፣ ምን ልታዘዝ ይላል… አንድ ማኪያቶ - ካንድ እሷ ጋር ልበል… አንድ ካፑችኖ - ካንድ እሷ ጋር ልበል… ከጥቁር ቡና ጋር - እሷን ...

ያላለቀ ድርሰት

ያላለቀ ድርሰት Written by   አንተነህ ይግዛው       “ኧረ ይብቃህ ደጀኔ!... አራት ሰዓት ሞላኮ!...” አሉ እትየ ስንዱ፣ መጋረጃውን ገለጥ አድርገው ከወደ ጓዳ ብቅ እያሉ፡፡ “አንቺ ግን ለምን ሰላም አትሰጪኝም!?...” ደጀኔ አቀርቅሮ ከሚጽፍበት ቀና በማለት በንዴት ጦፎ እስክርቢቶውን ወረወረ፡፡ “ስንቴ ልንገርሽ አክስቴ!?… በውስጤ የታመቀውን የደራሲነት ስሜት መተንፈስ እንጂ፣ የኮሌጅ ትምህርት አጠናቆ መመረቅ አይደለም የህይወቴ ጥሪ!” እየተንቀጠቀጠ ተናገረ፡፡ “የዛሬውስ የተለየ ነው!... ገና በማለዳ ንትርክ ጀመራችሁ?” የእማማ በለጡ ድምጽ በስተቀኝ ያለውን የኮምፔርሳቶ ግድግዳ አልፎ ተሰማ፡፡ ከጉዳይ የጣፋቸው አልነበረም፡፡ “ተው እንጂ ደጀኔ… ደህና ሂደህ ሂደህ አንድ አመት ሲቀርህ አትሰላች!” በትህትና መለሱለት፡፡ “አንቺኮ ችግርሽ ይሄ ነው!... የጀመርኩትን ትምህርት እንጂ፣ የጀመርኩትን ድርሰት ስለመጨረሴ አትጨነቂም!” ከተቀመጠበት ብድግ አለ፡፡ ሁለት አንቀጽ ጅምር አጭር ልቦለድ የጻፈባትን ወረቀት ከጠረጴዛው አንስቶ በፍጥነት ወደ ጓዳ አመራ፡፡ “እኔኮ ላንተ ብየ ነው!... ደሞም’ኮ አትጣፍ አላልኩህም፡፡ ከኮሌጅ ስትመለስ መጨረስ ትችላለህ” አሉት አክስቱ በትህትና ፈገግ ብለው፡፡ የአክስቱ ትህትና የገነፈለ ስሜቱን በረድ አደረገለት፡፡ እንደወትሮው አልተቆጡትም፡፡ እንደሌላው ጊዜ ልብ የሚሰብር ነገር አልተናገሩትም፡፡ “ደሞ አንተን ብሎ ደራሲ!... የአስር ሳንቲም ሻይ ቅጠል የማይገዛ እንቶፈንቶ መሞንጨሩን ትተህ፣ ትምህርትህን ብታጠና ይሻልሃል!” ብለው አልተሳለቁበትም፡፡ ወደ ጓዳ የጀመረውን ...