ወደ ዋና ይዘት ዘለው ይሂዱ

ልጥፎች

ያማል! ገጣሚ ሰለሞን ሳህለ

እንደነገርኩሽ… የሚወዱትን ሰው - ቀጥሮ እንደመጠበቅ፣ የነፍሰ ጡርን ሞት - አይቶ እንደመሳቀቅ፣ ባልታሰበ ናዳ - ተመትቶ እንደመድቀቅ፣ ከተስፋ ጉልላት - ተገፍቶ እንደመውደቅ፣ ታምር በበዛባት - በዚህች ቧልተኛ ዓለም፣ ከዚህ የበለጠ - ምንም ህመም የለም፡፡ አውቶብሱ ያማል፣ ሚኒባሱ ያማል፣ ላዳ ታክሲው ያማል፣ የማይጎል የሰው ጎርፍ ደራሽ ማዕበሉ፣ የእንባ ቅጥልጥሉ፣ ምን ብዬ ልንገርሽ - ያማል ይሄ ሁሉ፡፡ እና እንደነገርኩሽ… የሚወዱትን ሰው ቀጥረው ካረፈደ፣ የሚያፈቅሩትን ሰው ቀጥረው ካረፈደ፣ ነገር ተበላሸ - ህመም ተወለደ፡፡ ጨጓራ በገነ፣ እሳት በእንፋሎት መልክ በእህታ ተነነ፡፡ የሚሆነው ሳይሆን የማይሆነው ሆነ፡፡ ሁሉም ተቀይሮ ተተካ በሲቃ፣ ምን ብዬ ልንገርሽ ይህም ያማል በቃ፡፡ ወጪ ተራማጁ፣ አስመሳይ ሰጋጁ፣ ፀሐዩ ዝናቡ፣ የለምን ምክንያት የለምን ሰበቡ፣ ተቆራጭ አበባ ሊቆረጥ ማበቡ፣ ውል የለሽ ደመና ተራራ መክበቡ፣ እልፍ አዕላፍ ኮከብ ጨረቃን ማጀቡ፣ ደግሞ ለእሷ ግጥም እናቷን ጨረቃ፣ ምን ብዬ ልንገርሽ ይህም ያማል በቃ፡፡ እና እንደነገርኩሽ… ጉንጭ የማትሞላ ኬክ 10 ብር የሸጠ፣ የካፌ አሳላፊ ወደ እኔ አፈጠጠ፡፡ ዘይት የነካውን መንታ እጁን አጣምሮ፣ ምን ልታዘዝ ይላል ቁልቁል አቀርቅሮ፡፡ ምን ልታዘዝ ይላል… እንዴት ቅጥሉ ሰው ቅጥሉን ሰው ያዛል፣ ማኪያቶ ልዘዝ…? ካፑቺኖ ልዘዝ…? ጥቁ ቡና ልዘዝ…? ለምን ሰው አላዝም… መታዘዝ መናዘዝ ርግማን የሆነው፣ ካፌውን ሲያሳልፍ፣ ራሱ ግን የሚያልፍ፡፡ ቁልቁል አቀርቅሮ፣ ሞቱን ባንገት ቀብሮ፣ ምን ልታዘዝ ይላል… አንድ ማኪያቶ - ካንድ እሷ ጋር ልበል… አንድ ካፑችኖ - ካንድ እሷ ጋር ልበል… ከጥቁር ቡና ጋር - እሷን ...
የቅርብ ጊዜ ልጥፎች

ያላለቀ ድርሰት

ያላለቀ ድርሰት Written by   አንተነህ ይግዛው       “ኧረ ይብቃህ ደጀኔ!... አራት ሰዓት ሞላኮ!...” አሉ እትየ ስንዱ፣ መጋረጃውን ገለጥ አድርገው ከወደ ጓዳ ብቅ እያሉ፡፡ “አንቺ ግን ለምን ሰላም አትሰጪኝም!?...” ደጀኔ አቀርቅሮ ከሚጽፍበት ቀና በማለት በንዴት ጦፎ እስክርቢቶውን ወረወረ፡፡ “ስንቴ ልንገርሽ አክስቴ!?… በውስጤ የታመቀውን የደራሲነት ስሜት መተንፈስ እንጂ፣ የኮሌጅ ትምህርት አጠናቆ መመረቅ አይደለም የህይወቴ ጥሪ!” እየተንቀጠቀጠ ተናገረ፡፡ “የዛሬውስ የተለየ ነው!... ገና በማለዳ ንትርክ ጀመራችሁ?” የእማማ በለጡ ድምጽ በስተቀኝ ያለውን የኮምፔርሳቶ ግድግዳ አልፎ ተሰማ፡፡ ከጉዳይ የጣፋቸው አልነበረም፡፡ “ተው እንጂ ደጀኔ… ደህና ሂደህ ሂደህ አንድ አመት ሲቀርህ አትሰላች!” በትህትና መለሱለት፡፡ “አንቺኮ ችግርሽ ይሄ ነው!... የጀመርኩትን ትምህርት እንጂ፣ የጀመርኩትን ድርሰት ስለመጨረሴ አትጨነቂም!” ከተቀመጠበት ብድግ አለ፡፡ ሁለት አንቀጽ ጅምር አጭር ልቦለድ የጻፈባትን ወረቀት ከጠረጴዛው አንስቶ በፍጥነት ወደ ጓዳ አመራ፡፡ “እኔኮ ላንተ ብየ ነው!... ደሞም’ኮ አትጣፍ አላልኩህም፡፡ ከኮሌጅ ስትመለስ መጨረስ ትችላለህ” አሉት አክስቱ በትህትና ፈገግ ብለው፡፡ የአክስቱ ትህትና የገነፈለ ስሜቱን በረድ አደረገለት፡፡ እንደወትሮው አልተቆጡትም፡፡ እንደሌላው ጊዜ ልብ የሚሰብር ነገር አልተናገሩትም፡፡ “ደሞ አንተን ብሎ ደራሲ!... የአስር ሳንቲም ሻይ ቅጠል የማይገዛ እንቶፈንቶ መሞንጨሩን ትተህ፣ ትምህርትህን ብታጠና ይሻልሃል!” ብለው አልተሳለቁበትም፡፡ ወደ ጓዳ የጀመረውን ...
ከጥቁር ሰማይ ስር በእንዳለጌታ ከበደ ጥዋት ጥዋት፣ ወደ ቢሮ ለመሄድ - መታጠፊያው ጋ ሲደርስ - እተለመደ ቦታዋ ቁጭ ብላ የሚያጉተመትም በሚመስል ድምጿ ያለማቋረጥ ስታወራ ይሰማታል፡፡ የአራት ልጆች እናት የሆነችዋን የኔ ቢጤ፡፡ የእናታቸውን ያህል ባይሆንም ጎስቁለዋል፡፡ እንደ ምጣድ ማሰሻ የቀድሞ ከለሩ ያልታወቀ ከነቴራ ለብሰዋል - ከወገባቸው በላይ፡፡ ከመሃከላቸው አንዳቸውም ቃጭል አንጠልጥለው አልተወለዱም፡፡ . . . በማያውቀው ቋንቋ ታወራቸዋለች፡፡ ልጆቿ አይመልሱላትም፡፡ እርስ በርሳቸው ሲጨዋወቱ በአዲስ አበባ አማርኛ ነው የሚግባቡት፡፡ እንዲህ በከንቱ ጉንጭዋን የምታለፋው በውስጡ ያደረውን ጩዋሂ መንፈስ ላለማዳመጥ ይሆን? ብሎ ያስባል ጤንነቷን የማይጠራጠር የለም፡፡ አንዳንዶች ፥ ስለ ልጆቿ የወደፊት ዕጣ ፈንታ ማሰላሰል ስታበዛ ይሆን ያተሳሰብ ማዛንዋ የተዛባው? ይላሉ፡፡ ሁልጊዜ ያልተለመደ ነገር ስታደርግ ያጋጥመዋል፡፡ እጇ ላይ የተገኘን ማንኛውም ነገር ለአራት አካፋፍላ ለልጆች ታድላቸዋለች፡፡ ለራሷ የምታደርገው አይኖራትም፡፡ ከሲታ ናት ደግሞ፤ ያለ እህል ውሃ ለመኖር ሙከራ የጀመረች እስኪመስል ድረስ፡፡ ሳንቲም ተወርውሮ እግሯ ስር ያረፈ እንደሆነ ቅጭልጭልታውን ሰምታ እንኳን ቀና አትልም፡፡ ማንንም አይታይም - አገጯን ጉልበቷ ስር ደብቃ ነው፤ ቀኑን ውላ የምታመሸው፤ የምታነጋውም! መንገድ ዳር፡፡ እሷ ካለችበት ፈንጠር ብሎ - አንድ ክፉ የማይመስል - ዘባተሎ ለባሽ ጎልማሳ - በጠባቂነት መንፈስ ዓይኑን ያንከራትትባቸዋል፡፡ በየመንገዱ የሰበሰባቸው ቁርጥራጭ ሲጋራዎች ከኪሱ እያወጣ ያጨሳል፡፡ የልጆቿ አባት ይሆን? . . . ወይስ ወደ ጎዳና ከወጣች በኋላ የተወዳጃት ጊዜያዊ ባል?! . ...