ወደ ዋና ይዘት ዘለው ይሂዱ

ልጥፎች

ከ2017 ልጥፎች በማሳየት ላይ

ያማል! ገጣሚ ሰለሞን ሳህለ

እንደነገርኩሽ… የሚወዱትን ሰው - ቀጥሮ እንደመጠበቅ፣ የነፍሰ ጡርን ሞት - አይቶ እንደመሳቀቅ፣ ባልታሰበ ናዳ - ተመትቶ እንደመድቀቅ፣ ከተስፋ ጉልላት - ተገፍቶ እንደመውደቅ፣ ታምር በበዛባት - በዚህች ቧልተኛ ዓለም፣ ከዚህ የበለጠ - ምንም ህመም የለም፡፡ አውቶብሱ ያማል፣ ሚኒባሱ ያማል፣ ላዳ ታክሲው ያማል፣ የማይጎል የሰው ጎርፍ ደራሽ ማዕበሉ፣ የእንባ ቅጥልጥሉ፣ ምን ብዬ ልንገርሽ - ያማል ይሄ ሁሉ፡፡ እና እንደነገርኩሽ… የሚወዱትን ሰው ቀጥረው ካረፈደ፣ የሚያፈቅሩትን ሰው ቀጥረው ካረፈደ፣ ነገር ተበላሸ - ህመም ተወለደ፡፡ ጨጓራ በገነ፣ እሳት በእንፋሎት መልክ በእህታ ተነነ፡፡ የሚሆነው ሳይሆን የማይሆነው ሆነ፡፡ ሁሉም ተቀይሮ ተተካ በሲቃ፣ ምን ብዬ ልንገርሽ ይህም ያማል በቃ፡፡ ወጪ ተራማጁ፣ አስመሳይ ሰጋጁ፣ ፀሐዩ ዝናቡ፣ የለምን ምክንያት የለምን ሰበቡ፣ ተቆራጭ አበባ ሊቆረጥ ማበቡ፣ ውል የለሽ ደመና ተራራ መክበቡ፣ እልፍ አዕላፍ ኮከብ ጨረቃን ማጀቡ፣ ደግሞ ለእሷ ግጥም እናቷን ጨረቃ፣ ምን ብዬ ልንገርሽ ይህም ያማል በቃ፡፡ እና እንደነገርኩሽ… ጉንጭ የማትሞላ ኬክ 10 ብር የሸጠ፣ የካፌ አሳላፊ ወደ እኔ አፈጠጠ፡፡ ዘይት የነካውን መንታ እጁን አጣምሮ፣ ምን ልታዘዝ ይላል ቁልቁል አቀርቅሮ፡፡ ምን ልታዘዝ ይላል… እንዴት ቅጥሉ ሰው ቅጥሉን ሰው ያዛል፣ ማኪያቶ ልዘዝ…? ካፑቺኖ ልዘዝ…? ጥቁ ቡና ልዘዝ…? ለምን ሰው አላዝም… መታዘዝ መናዘዝ ርግማን የሆነው፣ ካፌውን ሲያሳልፍ፣ ራሱ ግን የሚያልፍ፡፡ ቁልቁል አቀርቅሮ፣ ሞቱን ባንገት ቀብሮ፣ ምን ልታዘዝ ይላል… አንድ ማኪያቶ - ካንድ እሷ ጋር ልበል… አንድ ካፑችኖ - ካንድ እሷ ጋር ልበል… ከጥቁር ቡና ጋር - እሷን ...